አዲስ አበባ፣ መሰከረም 23፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ሚሊየኖች የተሳተፉበት የሆራ አርሰዴ በዓል በተረጋጋ ሁኔታና ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቀረቡ፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ በዓሉ በሰላም መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ በሰጡት መግለጫ÷ የኢሬቻ ማክበሪያ ቦታ የእርቅ፣ የፍቅር እና የይቅርታ ቦታ እንጂ የጥላቻና የፖለቲካ መድረክ እንዳልሆነ የኦሮሞ ህዝብ በአንድነት አስመስክሯል ብለዋል፡፡