አዲስ አበባ፣ መሰከረም 23፣2014 (ኤፍ ቢሲ) መንግስት በእርዳታ ሽፋን የሀገርን ደህንነት አደጋ ላይ በሚጥል ህገ ወጥ ተግባር ተሰማርተው ባገኛቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰራተኞች ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ተገቢ እንደሆነ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አስታወቁ።
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ እንደገለጹት÷ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች በአንድ ሀገር ሰብዓዊና ቁሳዊ ችግሮች ሲፈጠሩ እገዛ ለማድረግ መግባታቸው የተለመደ ነው ፤ይህንን ተግባር ሲያከናውኑ ግን የሀገሪቱን ህግ የማክበር ግዴታ አለባቸው።