የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ምድር በአመፅና በጠመንጃ ትግል የሚገኝ ስልጣን እንደማይኖር ሊታወቅ ይገባል- ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

By Feven Bishaw

October 04, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)በኢትዮጵያ ምድር በአመፅና በጠመንጃ ትግል ወይም ንፁሃንን በማሻበር የሚገኝ ስልጣን ከእንግዲህ እንደማይኖር ሊታወቅ ይገባል ሲሉ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተናገሩ፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጋራ መክፈቻ ጉባኤ የተካሄደ ሲሆን ÷በሁለቱም ምክር ቤቶች የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ንግግር አድርገዋል፡፡