አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)በኢትዮጵያ ምድር በአመፅና በጠመንጃ ትግል ወይም ንፁሃንን በማሻበር የሚገኝ ስልጣን ከእንግዲህ እንደማይኖር ሊታወቅ ይገባል ሲሉ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተናገሩ፡፡
የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጋራ መክፈቻ ጉባኤ የተካሄደ ሲሆን ÷በሁለቱም ምክር ቤቶች የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ንግግር አድርገዋል፡፡