አዲስ አበባ፣መስከረም፣25፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር ኃይል በማዕከላዊ አየር ምድብ በሥራ አፈፃፀማቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ እና የመቆያ ጊዜያቸውን ለሸፈኑ የምድቡ የሠራዊት አባላት የማዕረግ እድገት ሠጠ፡፡
የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለሎጂስቲክ ብርጋዴር ጀነራል ነገራ ለሊሳ÷ አሸባሪው ቡድን የፈፀመውን ወረራ በመቀልበስ ረገድ አየር ኃይላችን ከፍተኛ ጀግንነት እየፈፀመ መሆኑን ተናግረዋል።