አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚደረጉ ድርድሮች ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ በሚያደርግ ስምምነት ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባቸው የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገለፁ።
የስትራቴጂክ ጉዳዮች ተቋም የሚያዘጋጀው ወርሃዊ ሴሚናር ላይ በዛሬው እለት “በህዳሴ ግድብ ዙሪያ እየተደረጉ ባሉ ድርድሮች” ላይ ትኩረቱን አድርጎ ተካሂዷል።