የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የዓሳ ጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከል ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ሊገባ ነው

By Tibebu Kebede

February 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የአሳ ጫጩት ማስፈልፈያ ማዕከል ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ሊገባ መሆኑን የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የክልሉ የባህር የአሳ እና ሌሎች የውሃ ውስጥ አካላት ምርምር ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ተዋበ እንዳሉት፥ በጣና ሃይቅ ላይ የሚስተዋለው የህገ ወጥ አሳ አስጋሪዎች እንቅስቃሴ የሃይቁን የአሣ ሃብት አሳሳቢ ደረጃ ላይ አድርሶታል።