አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዩ ልዑክ አምባሳደር ባርሊ ሻሮን ከተመራው የእስራኤል ከፍተኛ የመንግስት የልዑካን ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም አቶ ደመቀ ÷ሁለቱ ሀገራት በመከባበርና እና በጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው መሆኑን በማውሳት ይህንን ምቹ ሁኔታ በሀገራቱ በኢኮኖሚ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር መጠቀም አንደሚያስፈለግ ጠቁመዋል።