የሀገር ውስጥ ዜና

መኪና አስመጣላሁ በሚል ከ17 ሚሊየን ብር በላይ ከሰዎች ሰብስቦ ተሰወረ የተባለው ኩባንያ ምላሽ ሰጥቷል

By Tibebu Kebede

February 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) መኪና አስመጣላሁ በሚል ከግለሰብ 173 ሺህ ብር በላይ በድምሩ ከ17 ሚሊየን ብር በላይ ሰብስቦ ተሰወረ የተባለው ኩባንያ አለሁ ብሏል።

ፋት ትራንስፖርት ቴክኖሎጂስ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አሽከርካሪውን ጨምሮ 5 ሰዎችን የሚያሳፍር መኪና፣ በ30 በመቶ ቅድመ ክፍያ በ90 ቀናት ውስጥ አስረክባለሁ በማለት ከ102 ሰዎች ገንዘብ ተቀብሎ መሰወሩን ቅሬታ አቅራቢዎች ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።