አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፥ 2014 ዓ.ም( ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የአዕምሮ ጤና ተጠቂዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደሚገኝ በጤና ሚኒስቴር የፕሮግራም ሚኒስትር ዴኤታ ጽህፈት ቤት ሃላፊና አማካሪው አቶ ፍቃዱ ያደታ አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ የአዕምሮ ጤና ቀን በድሬደዋ ከተማ አዘጋጅነት “የአዕምሮ ጤናን ለሁሉም እውን እናድርግ” በሚል መሪ ቃል እየታሰበ ሲሆን፥ የሚታሰበውም በዓለም ለ30ኛ፥ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ10ኛ ጊዜ ነው።