የሀገር ውስጥ ዜና

በምስራቅ አፍሪካ የበረሃ አንበጣን ለመከላከል ዓለም አቀፍ ድጋፍ ተጠየቀ

By Tibebu Kebede

February 07, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት ዓለም አቀፍ ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ።

በአካባቢው የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ መከላከል ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት እና ገለፃ በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው።