የሀገር ውስጥ ዜና

የፍልስጤም ራስ ገዝ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ለጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላለፉ

By Feven Bishaw

October 15, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፍልስጤም ራስ ገዝ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሙሃሙድ አባስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላለፉ፡፡

ፕሬዚዳንት ሙሃሙድ አባስ ለኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት የለዉጥ እና የብልፅግና እንዲሆን መልካም ምኞታቸዉን መግለፃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡