አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ የሚገኙ የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማትን የሚያካትት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መክፈቱ ተገለጸ።
ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ትናንት ሲከፈት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ፀሐፊ ሊቀ-ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ በኬኒያ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ ዓለምና የኬኒያ የሃይማኖት የተቋማት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አባ ጆሴፍ ሙቲ መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።