አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊነት የበጎ አድራጎት ማህበር በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማና ወናጎ ወረዳ ለተቸገሩ ተማሪዎች ድጋፍ አደረገ፡፡
ማህበሩ ዋን ፓክ ፎር ዋን ቻየልድ (One pack For one child) በኩል ለማህበሩ በጌዴኦ ዞን ድጋፍ ለሚሹ 650 ተማሪዎች ከ200 ሺህ ብር በላይ በሚገመት ገንዘብ የትምህርት ቁሳቁስ ማበርከቱን ጠቁመው በቀጣይም በተቋም ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ የማህበሩ ሰብሳቢ ወጣት ነብዩ ፍቃዱ አስታውቀዋል፡፡