አዲስ አበባ፣ጥቅምት 9፤2014 (ኤፍ ቢሲ) በደብረ ብርሃን ከተማ የመነኩሴ ልብስ ለብሶ ሲያጭበረብር የነበረን አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የፅህፈት ቤቱ ቤት ኃላፊ ኮማንደር ታዬ ሀብተጊዮርጊስ እንደተናገሩት÷መስከረም 27 ቀን 2014 ዓ.ም በከተማው ቀበሌ 2 አካባቢ ከጠዋቱ 4 ሰዓት የመነኩሴ ልብስ ለብሶ የተለያዩ ተልዕኮዎችን ለመፈፀም ሲንቀሳቀስ የነበረን አንድ ግለሰብ ነው በማህበረሰብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር በማዋል መረጃ ሲጣራ የቆየው፡፡