አዲስ አበባ፣ጥቅምት 9፤2014 (ኤፍ ቢሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዲፕሎማቶች፣ ለሠራተኞቹና ለተጠሪ ተቋማት ሠራተኞች በሁለት ዙር ያካሄደው ሥልጠና መጠናቀቁን አስመልክቶ የመዝጊያ መርኃ ግብር በወዳጅነት አደባባይ እያካሄደ ነው።
በመርኃ ግብሩ ላይ የታደሙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እንደተናገሩት፤ ሠልጣኞቹ በቆይታቸው ተልዕኳቸውን በብቃት ለመፈጸም የሚያስችላቸውን ክህሎት ጨብጠዋል።