አዲስ አበባ፣ጥቅምት 9፤2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት የውሸት የስራ ሪፖርቶችን ለማስቀረት ህብረተሰቡን የሚያሳትፉ ስልቶችን ተግባራዊ ማድረግ አለበት ሲሉ ምሁራን ተናገሩ።
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ልማት ኢንስቲትዩት መምህር ዶክተር መሐመድ አሊና በጂማ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት ክፍል ባልደረባ እጩ ዶክተር ብርሃኑ ጌታቸው እንዳሉት ÷ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በሚያቀርቡት ሪፖርት ብቻ በስልጣን እንዲቀጥሉ መደረጉ የውሸት ሪፖርት እንዲበራከት በር ከፍቷል።