አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በነቀምት ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚኖሩ ተማሪዎች የምዕራብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የሰራዊት አባላት የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ፡፡
የምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ኮሎኔል ቢረሳው ሽፈራው ÷ ሰራዊቱ ግዳጁን በሚወጣበት አካባቢ ሁሉ ህዝባዊነቱን በተግባር የሚገለፅበትን ስራ እንደሚያከናውን ገልፀው ይህም አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል።