የሀገር ውስጥ ዜና

አራተኛው የቻይና የንግድ ትርኢት ለኢትዮጵያ ቡና ግብይት ሰፊ እድል ይዞ መጥቷል

By Feven Bishaw

October 26, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) አራተኛው ዙር የቻይና የውጭ ንግድ ትርኢት ለኢትዮጵያ የቡና ግብይት ሰፊ እድል ይዞ መምጣቱ ተነገረ።

በኢትዮጵያ ትልቁ የቡና አምራችና ላኪ ቅርንጫንፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ እስራኤል ደገፋ ከሺንዋ ጋር በነበራቸው ቆይታ ድርጅታቸው በትርኢቱ በመሳተፍ የኢትዮጵያን ባለ ልዩ ጣዕም እና ጥራት ያለው ቡና እንደሚያስተዋውቅ ገልጸዋል።