አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በተራድኦ ተቋማት ስም የሚንቀሳቀሱ ተቋማት በሃገር ሉአላዊነትና አንድነት ላይ ተጽእኖ እንዳያደርሱ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ሲሉ የህግና የታሪክ ምሁራን ተናገሩ፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ እና ታሪክ መምህር ዶክተር አልማዉ ክፍሌ÷ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች የሃገራትን የፖለቲካ ስንጥቃትን ተጠቅመው የግል ጥቅማቸውን ሲያስከብሩ እንደቆዩ ያብራራሉ ።