ጥቅምት 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሀና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት 714 ተማሪዎች ላይ ምርመራ ተደርጎ ምንም አይነት የምግብ መመረዝ ችግር እንዳላጋጠመ ተገለጸ።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ እንደገለጹት፥ በተካሄደው የህክምና በምርምራ ውጤቱ መሰረት ተማሪዎቹ የምግብ መመረዝም ሆነ ሌላ ምንም አይነት ሕመም እንዳልተገኘባቸው ተረጋግጧል።