የሀገር ውስጥ ዜና

የመከላከያ ሰራዊቱ  ዛሬም  ከፍተኛ  ተጋድሎ በማድረግ ላይ ይገኛል

By Feven Bishaw

October 31, 2021

አዲስ አበባ፣ጥቅምት 21፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ሰራዊቱ  ዛሬም  ከፍተኛ  ተጋድሎ በማድረግ ላይ ይገኛል  ሲል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ፡፡

በደሴ ግንባር የተከሰተውን ሁኔታ በማስመልከት ለጋዜጠኞች ማብራሪያ የሰጡት የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ÷ መከላከያ የሚወስዳቸውን ስልታዊ እርምጃዎች በተሳሳተ መንገድ በመገንዘብም ሆነ ህዝብን ለማደናገጥ የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ የህዝብ አንቂዎች እና ህዝብን የከዱ ባንዳዎችን መንግሥት ፈፅሞ አይታገስም ብለዋል፡፡