አዲስ አበባ፣ጥቅምት 21፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ሰራዊቱ ዛሬም ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ ላይ ይገኛል ሲል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ፡፡
በደሴ ግንባር የተከሰተውን ሁኔታ በማስመልከት ለጋዜጠኞች ማብራሪያ የሰጡት የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ÷ መከላከያ የሚወስዳቸውን ስልታዊ እርምጃዎች በተሳሳተ መንገድ በመገንዘብም ሆነ ህዝብን ለማደናገጥ የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ የህዝብ አንቂዎች እና ህዝብን የከዱ ባንዳዎችን መንግሥት ፈፅሞ አይታገስም ብለዋል፡፡