አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከካናዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንስዋ ፍሊፕ ሻምፐኝ ጋር ተወያዩ።
በውይይቱም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ እንደገለፁት፥ ኢትዮጵያና ካናዳ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውሰው፤ ካናዳ በኢትዮጵያ ልማት ዙሪያ ጠንካራ አስተዋፅኦ ካደረጉ ሀገሮች አንዷ መሆኗን ገልጸዋል።