የሀገር ውስጥ ዜና

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ህወሓት እየፈፀመ ያለውን ሽብር ሊያወግዝ ይገባል – አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

By Feven Bishaw

November 04, 2021

አዲስ አበባ፣ጥቅምት 25፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከዴንማርክ አምባሳደር ኪራ ስሚዝ ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱ ላይ ኢትዮጵያ አሁን ላይ ላጋጠማት ችግር ዋና ተጠያቂው ህወሓት መሆኑን አምባሳደር ሬድዋን አብራርተዋል።