አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀረሪ ክልል ለተቋቋመው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ ቀጣይ ስራዎችን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ስምሪት ተሰጥቷል።
የሃረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በአገር አቀፍ ደረጃ የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መነሻ በማድረግ ለምስራቅ ዕዝ ዋና መምሪያ እና ለምስራቅ ሀረርጌ ዞን በቅንጅት መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዩች ላይ ውይይት በማድረግ እና የሥራ መመሪያ በመስጠት ወደ ተግባር እንዲገቡ የሚያስችል አቅጣጫ አስቀምጠዋል።