አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአገር ሕልውናና ሉዓላዊነት ላይ የተደቀነውን አደጋ ለመከላከል ተግባራዊ የሆነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተፈጻሚነት የበኩላቸውን እንደሚወጡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ።
የምክር ቤቱ አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በኢትዮጵያ ላይ የተከፈቱ የወታደራዊ፣ የምጣኔ ሃብትና የፕሮፓጋንዳ ጦርነቶች የአገር ሕልውናን እንደሚፈታተኑ ገልጸዋል።