አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)”ኢትዮጵያን አፍርሼ እረማመድባታለሁ” ብሎ የተነሳውን አሸባሪ ቡድን በጋራ ክንዳችን እናፈርሰዋለን ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ተናገሩ።
ኢትዮጵያዊያን ለ27 አመታት ግፍና በደሉን ተሸክመው ቆይተው መከራው ሲበረታባቸው “በቃህ” ብለው ያስወገዱት አሸባሪው ህወሃት “ኢትዮጵያን ሳላፈርስ ወደ ሲኦል አልገባም” በማለት የቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ይገኛል።