አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወያኔና ሸኔ ያላቸው ጥምረት የሚቀጥለው የወያኔን የበላይነትና የገዥነት ባህሪ መሸከም እስከቻለ ጊዜ ድረስ ብቻ ነው ሲሉ አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ።
አቶ ሽመልስ ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ እብሪተኛው ወያኔ የኦሮሞን አቅም ስለሚያውቅ በኦሮሞ ላይ ትኩረት አድርጎ በመንቀሳቀስ ባለፉት 27 ዓመታት የራሱን የበላይነት ለመጫን ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡