የሀገር ውስጥ ዜና

የወያኔና የሸኔ ጥምረት የሚቀጥለው የወያኔን የበላይነ መሸከም እስከቻለ ጊዜ ድረስ ብቻ ነው – አቶ ሽመልስ አብዲሳ

By Feven Bishaw

November 05, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወያኔና ሸኔ ያላቸው ጥምረት የሚቀጥለው የወያኔን የበላይነትና የገዥነት ባህሪ መሸከም እስከቻለ ጊዜ ድረስ ብቻ ነው ሲሉ አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ።

አቶ ሽመልስ ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ እብሪተኛው ወያኔ የኦሮሞን አቅም ስለሚያውቅ በኦሮሞ ላይ ትኩረት አድርጎ በመንቀሳቀስ ባለፉት 27 ዓመታት የራሱን የበላይነት ለመጫን ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡