አዲስ አበባ፣ጥቅምት 28፣2014 (ኤፍ ቢሲ)በመስቀል አደባባይ የተካሄደው ህዝባዊ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
“ሀገሬን እጠብቃለሁ መስዋዕትነት እከፍላለሁ” በሚል መሪ ቃል ህዝቡ ከመከላከያ ጎን መቆሙንና አሸባሪዎቹን ህወሃት እና ሸኔ ቡድኖች የሚያደርጉትን የጥፋት እንቅስቃሴ ለማውገዝ በአዲስ አበባ ከተማ የተካሄደው ህዝባዊ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።