አዲስ አበባ፣ ህዳር 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር ለህልውና ዘመቻው የሚሆን ከ7 ሚሊየን ብር በላይ ሃብት በማሰባሰብ አስረከበ፡፡
የወረዳው አስተዳደር ለህልውና ዘመቻው ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ለማሰባሰብ አቅዶ እስካሁን 6 ሚሊየን ብር የሚገመት ደረቅ ሬሽን፣ 1 ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ በአጠቃላይ 7 ሚሊየን ብር የሚገመት ሃብት በማሰባሰብ ማስረከብ መቻሉን የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳዊት ብርሃኑ ተናግረዋል፡፡