የሀገር ውስጥ ዜና

የዞኑ ህዝብ ለህልውና ዘመቻ ከ7 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

November 12, 2021

 

አዲስ አበባ፣ህዳር 3፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የምስራቅ ሸዋ ዞን ህዝብ መንግስት በቅርቡ ያቀረበውን የክተት ጥሪውን በመቀበል ለህልውና ዘመቻው በጥሬ ገንዘብ ከ7 ነጥብ 4 ሚሊየን ብርና ሌሎች የአይነት ድጋፍ ማድረጉን አስተዳዳሩ አስታወቀ።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባቡ ዋቆ ለኢዜአ እንደገለጹት መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የጸጥታ ሀይሎች ሀገር ለማዳን ውድ ህይታቸውን እየገበሩ ይገኛሉ።