የሀገር ውስጥ ዜና

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ለመከላከያ ሠራዊትና ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አደረጉ

By Feven Bishaw

November 12, 2021

 

አዲስ አበባ፣ህዳር 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ለመከላከያ ሠራዊትና ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ35 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከክፍለ ከተማው ነዋሪዎች የተሰበሰበውን የገንዘብ እና የአይነት ድጋፉን ተረክበው ለመከላከያ ሰራዊት ተወካዮች አስረክበዋል ።