የሀገር ውስጥ ዜና

በዳውንት መስመር ቆርጦ ወደ ታች ጋይንት ለመግባት የሞከረው ጠላት ኪሣራ እየደረሰበት ነው

By Feven Bishaw

November 12, 2021

 

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 3 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ይርጋ ሲሳይ በተለይ ለአሚኮ እንደገለጹት ጠላት ከሰሞኑ በዳውንት መስመር አድርጎ በታች ጋይንት ወረዳ በኩል ቆርጦ ለመግባት ሙከራ አድርጓል።

ይሁን እንጂ ሕዝቡንና የታጠቀውን ሃይል በማነቃነቅ የጠላትን እንቅስቃሴ መገደብ እንደተቻለና ጠላትም ኪሳራ እየደረሰበት መሆኑን ነው አቶ ይርጋ የተናገሩት።