የሀገር ውስጥ ዜና

ሚኒስቴሩ 15 ሚሊየን ለሚሆኑ ማሳዎች የ2ኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መስጠቱን ገለጸ

By Tibebu Kebede

February 11, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የግርብርና ሚኒስቴር 15 ሚሊየን ለሚሆኑ ማሳዎች የ2ኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር በማዘጋጀት ለአርሶ አደሮች መስጠቱን አስታወቀ።

በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰው የ˝ካልም ፕሮጀክት˝ በኢትዮጵያ የአርሶ አደር 2ኛ ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መስጠት የሚስችለውን ፕሮግራም ለማስጀመር በባህር ዳር ከተማ ውይይት እያካሄደ ነው።