የሀገር ውስጥ ዜና

የሁለት ሚሊየን ኩንታል ስኳር ግዥ ተፈጽሟል

By Feven Bishaw

November 18, 2021

 

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የስኳር አቅርቦት እጥረትን ለማሻሻል የሁለት ሚሊየን ኩንታል የስኳር ግዥ መፈፀሙን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የንግድ ዕቃዎች ዋጋ ጥናትና ክትትል ቡድን መሪ አቶ አሸናፊ ማሙየ እንደገለጹት÷ ከውጭ ሀገር ግዥ የተፈፀመበት 1 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ወደ ሀገር ውስጥ ገብቷል፡፡