አዲስ አበባ ፣ ህዳር 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ በንብረት ግምጃ ቤት ውስጥ የተቀመጡ ከ1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በህዝብ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ብርበራ ተያዙ፡፡
በቤተ ክህነቱ ግቢ በሚገኝ የንብረት ግምጃ ቤት በሚገኝ የፅህፈት እና የፅዳት እቃዎች ማስቀመጫ ውስጥ በተደረገው ብርበራ የተገኙት 1 ሺህ 363 የብሬን እና 493 የሽጉጥ ጥይቶች ናቸው፡፡