የሀገር ውስጥ ዜና

በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 5 ሚሊየን ብር ተያዘ

By Feven Bishaw

November 19, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ አርሲ ዞን በኮፈሌ ከተማ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 5 ሚሊየን ብር መያዙን የወረዳው ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዲቪዥን አስተባባሪ ዋና ሳጅን በዳሶ ጉደታ ገለፁ፡፡

በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ብር የተያዘው ከሻሸመኔ ከተማ ወደ ነንስቦት ከተማ ሊተላለፍ ሲል በኦሮሚያ ልዩ ፖሊስና በኮፈሌ ከተማ ፖሊስ ጥምረት ነው፡፡