አዲስ አበባ፣ ህዳር 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሙዩኒኬሽን እና የመገናኛ መሳሪያዎች በእጃቸው የሚገኝ ግለሰቦች እና ተቋማተ በ15 ቀናት ውስጥ እንዲያስመዘግቡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አሳሰበ።
በኢትዮጵያ ህልዉና አደጋን ለመከላከል፣ ስጋት እና ሉአላዊነት ጥሰት ለመከላከል ሁሉን አቀፍ የጥንቃቄ እርምጃዎች መዉስድ አስፈላጊ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ገልጿል፡፡