የሀገር ውስጥ ዜና

ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት የሚቃወም ሰልፍ በካናዳ ተካሄደ

By Feven Bishaw

November 21, 2021

አዲስ አበባ፣ ህዳር 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት ለመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጠራው ‘#NOMORE’ ዘመቻ ሰልፍ በካናዳ ኦቶዋ ተካሄደ፡፡

በሰልፉ ላይ በካናዳ ኦቶዋ፣ ቶሮንቶ፣ ሞንትሪያል፣ ኩቤክ፣ ስካርብሮ፣ ኪንግስተን እና ሌሎች ከተሞች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላትና የኤርትራ ዜጎች ተሳትፈዋል፡፡