የሀገር ውስጥ ዜና

በምርት ዘመኑ በመኸር ልማት 13 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ ነው

By Feven Bishaw

November 22, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2013/14 የምርት ዘመን በመኸር ልማት 13 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ።

የመንግስት ኮሙኒኬሽ አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ሰላማዊት ካሳ በሰጡት መግለጫ፥ በ2013/14 የምርት ዘመን በመኸር ልማት 13 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡