የሀገር ውስጥ ዜና

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ አገሩን ለመታደግ ወደ ግንባር ለመዝመት ወሰነ

By Feven Bishaw

November 23, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሪ ተከትሎ አገሩን ለመታደግ ወደ ግንባር ለመዝመት መወሰኑን አስታውቋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔ ትክክል ነው ያለው አትሌት ፈይሳ በዚህ ሰአት በአገራችን ላይ የተቃጣውን ችግር ልክ አባቶቻችን በዓድዋ እንዳደረጉት እኔም በግንባር ሄጄ የሚጠበቅብኝን እወጣለው ማለቱን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡