አዲስ አበባ፣ ህዳር 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አለማፍረስ የመጣን ጠላት በግንባር ለመፋለም ዛሬ ማቅናታቸው ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት መከበር የገቡትን ቃል በተግባር ያሳዩበት የታሪክ ምዕራፍ ነው ሲሉ የፖለቲካ ዘርፍ ምሁራን ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መከላከያን በግንባር ሆኜ ለመምራት ወደ ትግሉ ሜዳ እዘምታለሁ ማለታቸው የሚታወስ ሲሆን÷ ለኢትዮጵያ የግዛት አንድነት ፣ ነጻነትና ሉዓላዊነት የሚከፈል ዋጋ እንደመሆኑ ግንባር ሁላችንም እንገናኝ ብለዋል ።