አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2014 የምርት ዘመን ሀገራዊ የበጋ የስንዴ መስኖ ልማት ይፋዊ የዘር ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በጋሞ ዞን የጋሞ ልማት ማህበር አርባ ምንጭ የእርሻ ልማት ላይ እየተካሄደ ነው።
ሀገራዊ የበጋ ስንዴ ልማት በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ አካባቢዎች ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን÷ እንደ ሀገር 400 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ በስንዴ እንደሚለማ ተጠቁሟል።