የሀገር ውስጥ ዜና

ለአፋር ሕዝብ ጠላትን የሽንፈት ካባ ማከናነብ አኩሪ የጀግንነት ባሕሉ ነው

By Feven Bishaw

November 26, 2021

 

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለአፋር ሕዝብ ጠላትን የሽንፈት ካባ አከናንቦ መመለስ ጥንትም የነበረ አኩሪ የጀግንነት ባሕሉ ነው ሲሉ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ሙሳ አደም ገለጹ፡፡

አሸባሪው የህወሓት ቡድን ሰርጎ በገባባቸውና ወረራ በፈጸመባቸው የአፋር አካባቢዎች የፀጥታ መዋቅሩና ሕዝቡ ባደረጉት የተቀናጀ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ሠብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበት ወደ መጣበት ተመልሷል።