አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ አርሲ ዞን ሄበን አርሲ ወረዳ ከአሸባሪው ሸኔ ጋር ግንኙነት ያላቸው 33 ሰዎች ከ7 ቀበሌዎች በይቅርታ ወደ ህዝቡ ተቀላቀሉ።
ከአሸባሪ ቡድኑ ጋር ግንኙነት ያላቸው እነዚህ ሰዎች አሸባሪዎቹ ትህነግና ሸኔ ጋብቻ ፈፅመው በአገር ላይ ጦርነት መክፈታቸው ፍፁም ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ አጀንዳቸውም የጥፋት መሆኑን ተረድተን ወደ ህዝባችን ተመልሰናል ብለዋል።