የሀገር ውስጥ ዜና

ወደ ግንባር ለሚዘምቱ የኢዜማ አመራሮች ሽኝት ተደረገ

By ዮሐንስ ደርበው

November 26, 2021

የኢዜማ መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከዚህ ቀደምም የተለያዩ የኢዜማ አባላት ወደ ግንባር መሄዳቸውን ገልጸው የሄዱት ግን ኢዜማ ስለሆኑ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ ስለሆኑ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የሁላችንም ግዴታ ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፥ እዚህ የተቀረው አባልና ሌሎች ኢትዮጵያውያንም ለዘማቾች ስንቅ በማዘጋጀት ደጀን እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።