የሀገር ውስጥ ዜና

በብሔር ስም እየነገዱ ኢትዮጵያን ማሸበር ፈጽሞ አይቻልም – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

By Feven Bishaw

November 26, 2021

 

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “ሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳ በመንዛትና በብሔር ስም በመነገድ ኢትዮጵያን ማሸበር ፈጽሞ አይቻልም” ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አበቤ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከኢትዮጵያ ባለፈ የአፍሪካ ርዕሰ መዲና እና የዓለም ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ማዕከል የሆነችውን አዲስ አበባ በፕሮፓጋንዳ ለማሸበር የሚደረጉ ጥረቶች የሕልውና ዘመቻው ከመጀመሩ በፊት የነበሩ ናቸው ብለዋል።