አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተደረገ ሰላም ማስከበር ዘመቻ የአሸባሪው ሸኔ አባላት ከእነትጥቃቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የዞኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
በዞኑ የዕዝ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ አብርሃም ጋዲሣ እንደገለፁት፥ የአሸባሪው ሸኔ አባላት ከእነትጥቃቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት ባለፉት አስር ቀናት የፀጥታ ሀይሎች ተቀናጅተው ባደረጉት የፀጥታ ማስከበር ዘመቻ ነው፡፡