አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው ህወሓት ለከፋ ችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት ለማቋቋምና የወደሙ አካባቢዎችን መልሶ ለማደራጀት ርብርብ እንደሚያደርጉ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተናገሩ፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከንግዱ ማህበረሰብ እና ከግል ሴክተሩ አንቀሳቃሾች ጋር ውይይት አካሂደዋል።
በውይይታቸው፥ በመጀመሪያው ዙር የህልውና ዘመቻ ላይ በደጀንነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያበረክት የነበረው የንግዱ ማህበረሰብ እና የግሉ ሴክተር ድጋፍን በማጠናከር በቀጣይ ዘላቂ አገራዊ ሰላምና የኢኮኖሚ መነቃቃትና ዕድገት ማረጋገጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

