Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ቻይና በአምስት አሜሪካውያን ላይ አጸፋዊ ማዕቀብ ለመጣል ወሰነች

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በአምስት አሜሪካውያን ላይ አጸፋዊ ማዕቀብ ለመጣል መወሰኗን የሃገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዣኦ ሊጂያን ገለጹ፡፡

ቃል አቀባዩ የአሁኑ የቻይና ማዕቀብ አሜሪካ በሐምሌ ወር በቻይና ባለሥልጣናት ላይ ለጣለችው ማዕቀብ ምላሽ መሆኑን አስታውቀዋል።

አሜሪካ የቻይና ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ የጣለችው ከሆንግ ኮንግ አስተዳደር ጋር በተያያዘ ተፈጽሟል ባለችው ፖለቲካዊ ሴራ ውስጥ ተሳትፋችኋል በሚል መሆኑን ም አስታውሰዋል፡፡

ቻይና አሜሪካን ከዚህ በኋላ በውስጥ ጉዳያችን እንዳትገቢ ስትል ማስጠንቀቋም የሚታወስ ነው።

ጣልቃ የምትገባ ከሆነ ግን ጥቅምና ክብሯን ለማስጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች ሲል ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version