Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኙ 3 ኩባንያዎች ምርታቸውን ወደ ውጭ መላክ ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በህወሓት የሽብር ቡድን ጉዳት ደርሶባቸው ከነበሩትና በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሥር የሚገኙት ሦስት ኩባንያዎች ምርታቸውን ወደ ውጭ ገበያ ማቅረብ ጀመሩ፡፡

በፓርኩ ከሚገኙት አራት ኩባንያዎች ሦስቱ ስራ መጀመራቸው የተገለጸ ሲሆን÷ ምርታቸውን ለውጭ ገበያ ማቅረብ መጀመራቸውም ተገልጿል።

አዲዳስ እና ፑማ ለመሳሰሉ አለም አቀፍ ተቋማት ምርቶቹ የሚያቀርቡ መሆኑን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የገለጹት የኩባንያው ስራ አስኪያጅ ዎልተር ፎድሊ÷ ከ5 ሚሊየን ዶላር በላይ ውድመት ቢደርስብንም በቶሎ ወደ ስራ ገብተናል ብለዋል።

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስራ አስኪያጁ አቶ ሙሉጌታ መኮንን በበኩላቸው የቀረው አንድ ኩባንያ በቅርቡ ስራ እንደሚጀምር ገልጸው ÷ 24 ሰዓት በማምረት ለውጭ ገበያ ምርቶች እየቀረቡ መሆኑንም ተናረዋል።

በፓርኩ ውስጥ ከሦስት ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው የተገለጸ ሲሆን÷ በሦስቱ ተቋማት ውስጥ የሚሠሩ ከ90 በመቶ በላይ ሰራተኞች ወደ ስራ መመለሳቸውም ተመላክቷል።

በጣሊያን፣ በአሜሪካ፣ በቻይና ፣ በደቡብ ኮሪያና በኢትዮጵያውያን ባለሀብቶች የተያዙት ኩባንያዎቹ÷ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት በኩል ሰፊ ስራ ሲሰሩ መቆየታቸውም ተገልጿል፡፡

ከሐምሌ እሰከ መስከረም ባሉት ሦስት ወራት ከ3 ነጥብ 9 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ አስገኝተዋል ነው የተባለው፡፡

ካርቪኮ ኢትዮጵያ ተሰኘው ኩባንያ 69 በመቶ የሚሆነውን ገቢ የሸፈነ መሆኑም ተገልጿል።

በከድር መሀመድ

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version